Passt nicht? Macht nichts! Bei uns ist die Rückgabe innerhalb von 30 Tagen möglich
Mit einem Geschenkgutschein können Sie nichts falsch machen. Der Beschenkte kann sich im Tausch gegen einen Geschenkgutschein etwas aus unserem Sortiment aussuchen.
30 Tage für die Rückgabe der Ware
ወደ እርስዋ ቀርቦ ውኃ አጠጪኝ አላት፤ አባ ጊዮርጊስ "አንተ የሕይወት ውኃ ስትሆን ከሳምራዊትዋ ሴት ውኃን ለመንህ" እንዳለ የሕይወት ውኃ ክርስቶስ ውኃ ለመናት፡፡ እርሱ የተጠማው ውኃ ሳይሆን የእርስዋን ነፍስ ነበረ፡፡ እርስዋም አንተ አይሁዳዊ ስትሆን ሳምራዊት ከምሆን ከእኔ ውኃ ትለምናለህ? አለችው፡፡ እንዲህ ነው ነገሩ፡፡ የቆሰለች ነፍስ ስለ ዘር ታወራለች፡፡ ተስፋ የቆረጠች ነፍስ የዘር ጉዳይ ሲሆን ልሳንዋ ይከፈታል፡፡ ውኃ ለማጠጣት ዘር መጠየቅን ምን አመጣው፡፡ ውኃው አይሁዳዊ ነው? ወይንስ ሳምራዊ? ውኃ ጠማኝ የሚል ሁሉ ውኃ ይገባዋል እንጂ ዘሩ አይጠየቅም፡፡ እርስዋ ግን ጠየቀችው፡፡ በእርግጥ ይህች ሳምራዊት ሴት ይህን ጥያቄ የጠየቀችው ክርስቶስ መሆኑን ከማወቅዋ በፊት ነበር፡፡ክርስቶስ መሆኑን ካወቀች በኋላ ግን ስለ አይሁዳዊነትና ስለ ሳምራዊነት ስትናገር አልተሰማችም፡፡ "አንተ አማራ ስትሆን ጉራጌ ከምሆን ከእኔ ውኃ ለምን ትለምናለህ?" "አንቺ ኦሮሞ ስትሆኚ ትግሬ ከምሆን ከእኔ እንዴት ውኃ ትለምኛለሽ?" በሚል ጥያቄ ሀገሩን ያጨናነቁተ ክርስቶስን ያወቁ ክርስቲያኖች መሆናቸው ግን ልብን የሚሰብር እውነታ ነው፡፡ በዚህ ጠባያችን እንደ ክርስቲያን ሳንኖር እንደ ክርስቲያን ልንሞት መሆኑ ምንኛ ያሳዝናል?
/ከውስጥ ገጽ የተወሰደ/
ይህ መጽሐፍ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ያዘጋጃቸው ልዩ ልዩ መጣጥፎችን ይዟል፡፡
ክፍል አንድ
ልዩ ልዪ ስብከቶች
የኤፍራጥስ ወንዝ /6/፣ እግዚአብሔር እንዴት ይፈርዳል? /21/፣ የካም ትውልድ /31/፣ ደስ ይበላችሁ /42/፣ ጌታ ሆይ ይህን ውኃ ሥጠኝ /49/፣ በገነት ያሉ ሦስት አስደናቂ ነገሮች /54/፣ ጌታ ሆይ እኔ እሆንን? /55/፣ የትሕትና ትምህርት ቤት /58/፣ እንዴት ወድቀን እንዴት ተነሣን? /66/፣ ሁለቱ መታጠቢያዎች /71/፣ ለማንም እንዳትናገር /74/፣ አባቶቻችን እንዲህ እንዲህ አሉ /79/፣ በሰንበት መፍረስ /91/፣ ዛሬ ነገ ነው? /93/፣ መርጦ መወለድ /96/፣ ኮሜድያኑ ሰማዕት /98/፣ ባለጸጋ ነዳያን /99/፣ ስሞት ዓይኔን የሚከድንልኝ ማን ይሆን? /105/፣ የግርፊያ ሰልፍ /110/፣ ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብታቸው /117/፣ ቤተ ክርስቲያንና ሚሽነሪዎች /121/
ክፍል ሁለት
የበዓላት ስብከቶች
ዘልደት
የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? /126/
ዘጥምቀት
መጥምቁ ዮሐንስን ማን አጠመቀው?/131/
ታኅሣሥ ገብርኤል
ከክርስቶስ በፊት የነበሩ ክርስቲያኖች /140/
ጾመ ነነዌ
ጣዕም የሌለው ስብከት /151/
ዘኒቆዲሞስ
በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጣ /158/
ዘሆሳዕና
ንጉሥ በአህያ ላይ /161/፣
የትንሣኤ ስብከቶች፣
፩ አትክልተኛ መስሏት ነበር /164/፣ ፪ ከሁሉ በኋላ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ታየኝ /171/፣ ፫ ፍቅር ቁስል ነው /178/
ዘጰራቅሊጦስ
የግንቦት ልደታ
የደብረ ታቦር ስብከቶች
Hallo! Ich bin Libroamiko, dein Buchberater.
Wie kann ich dir helfen?